ለሊቨርፑል መካነ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ኃይማኖት ቤ/ክ የተሰጠው የውጤታማ ሥራ አመራር ስልጠና ተጠናቀቀ

ለሰባት ተከታታይ ሳምንታት በበይነ መረብ የተሰጠው የውጤታማ ሥራ አመራር ስልጠና በትናንትናው እለት ተጠናቅቋል። በስልጠናው የተለያዩ መሰረታዊ ጉዳዮች የተዳሰሱ ሲሆን ስልጠናው በገለጻ፣ ውይይት እና ተግባራዊ እንቅስቃሴ የተደገፈ እንደነበር ታውቋል። የተሸፈኑት ዋና ዋና አርእስት፦ የኢ/ኦ/ተ/ቤ፣ ባህል እና የለውጥ አመራር፣ ባህል እና የለውጥ አመራር፣ ውጤታማ ተግባቦት፣ ውጤታማ ስብሰባ፣ በእቅድ መመራት እና የአሰራር መመሪያ ዝግጅት እንደሆኑ ታውቋል።

በመርሐግብሩ ማጠቃለያ ላይ የደብሩ አስተዳዳሪ ሊቀትጉኃን ቀሲስ ብርሃኑ ደሳለኝ ይህ የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ እድለኛ ነው። ውጤታማ ሥራን ለመስራት እና የበለጠ ለማገልገል የሚረዱ ክህሎቶችን ያስተዋወቀ ስልጠና አግኝቷል ብለዋል። እንዲሁም ለመርሐግብሩ ዝግጅት ቁልፍ የማስተባበር ስራን የሰሩት ቀሲስ ተመስገን ቅጣው ሰልጣኞች በስልጠናው ያገኟቸውን እውቀቶች በስራ ለመተግበር ሶስት ነገሮች ፡- ቁርጥ ውሳኔ፣ ትግበራ እና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን መሻገር፣ ወደቀደመ አሰራሮች ላለመመለስ መታገል ያስፈልጋል ብለዋል

በመርሐግብሩ መዝጊያ ላይ አጥቢያ ዶት ኮም የስልጠናውን ቀጣይ ትግበራ የማገዝ እና የመከታተል ስራን የሚሰራ ሲሆን በቀጣይነትም ሌሎች ጉዳዮች ላይ ተመሳሳይ መርሐግብሮች ቀርጾ እንደሚንቀሳቀስ ተገልጿል።