ቴክኖሎጂ ለቤተክርስቲያን
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የሚያመጣቸውን መልካም አጋጣሚዎች ለቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮ ማስፈጸሚያነት ለማዋል እንዲሁም ተግዳሮቶችን ለመቋቋም አጽንዖት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል።
በቴክኖሎጂ የተደገፈ ውጤታማ ተቋም ለመገንባት የግንዛቤ ማስጨበጫ፣ የመነሻ ጥናት፣ የግብአት ዝግጅት፣ የአተገባበር ስልት እና ቀጣይ ሞያዊ ድጋፍ ሊያስፈልግ ይችላል።
አጥቢያዎች ከምእመናን ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማዘመን በሁሉም ዘርፎች የተቀላጠፈ አገልግሎትን ለመስጠት እንዲያስችል ታልሞ ይህ መተግበሪያ ተዘጋጅቶልዎታል።
ስለአጥቢያ ዶት ኮም፣ ስለአገልግሎቶቻችን እና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ጥቆማወይም አስተያየትዎን ያካፍሉን። እርዳታ ቢያስፈልግዎም በፍጥነት ያሳውቁን።