በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ድረ-ገጽ ተለቀቀ

የሀገረ ስብከቱ ድረገጽ በብጹዕ አቡነ ኤርሚያስ ቡራኬ ዛሬ ሰኔ 6 ቀን 2015 ዓ.ም. ስራ ጀምሯል።

ድረገጹ የሀገረ ስብከቱን መሠረታዊ መረጃዎች፣ ወቅታዊ እንቅስቃሴዎች እና ሌሎች ስልታዊ ይዘቶችን ለህዝበ ክርስቲያኑ ለማድረስ ታልሞ የተሰራ እንደሆነ ታውቋል። ብጹዕ አቡነ ኤርሚያስ በማሳያ መርሐግብሩ ላይ በቴክኖሎጂ በመደገፍ ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለመስጠት የባለሞያዎች አስተዋጽዖ ወሳኝ እንደሆነ አጽንዖት ሰጥተው አባታዊ ምክራቸውን ለግሰዋል።

የሀገረ ስብከቱን ድረገጽ ይመልከቱ