የድረገጽ አስተዳደር ሥልጠና ተሰጠ

አጥቢያ ዶት ኮም በቅርቡ ሰርቶ ያስረከበውን የስዊድን፣ ስካንዲናቭያና የግሪክ ሀገሮች ሀገረ ስብከት ድረገጽ የማስተዳደር ሥልጠና ሀገረ ስብከቱ የአይ.ሲ.ቲ. /Information Communication Technology/ ክፍል አባላት ትናንት ኅዳር 22 ቀን 2015 ዓ.ም. ተሰጠ።

በሥልጠናው የአይ.ሲ.ቲ. ክፍሉ በአጥቢያ ዶት ኮም አጋዥነት ያዘጋጀው የድረገጽ አስተዳደር መመሪያ ላይ ገለጻ የተደረገ ሲሆን ድረገጹ ስለሚመራበት የተለያዩ የትግበራ ሂደቶች ውይይት ተደርጓል። በቀጣይም የድረገጹ መተግበሪያ ዝርዝር ሥልጠና የተሰጠ ሲሆን ከባለሞያዎች ለተነሱ ጥያቄዎችም ምላሽ ተሰጥቷል። በመርሐግብሩ ሁለት ካህናት አባቶች በመገኘት መርሐግብሩን የባረኩ ሲሆን ጥሩ ጅማሮ መሆኑን እና ከዚህም በላይ መስራት እንደሚገባ በመግለጽ የማበረታቻ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።