የማኅበረ ቅዱሳን የ2015 ዓ.ም. ግቢ ጉባኤያት ተመራቂዎች ዲጅታል መጽሔት ስራ ተጀመረ

አጥቢያ ዶት ኮም የዚህን ዓመት /2015 ዓ.ም./ የማኅበረ ቅዱሳን ግቢ ጉባኤ ተመራቂዎች ዲጅታል መጽሔት ዝግጅት ስራን ጀምሯል።

የትግበራ ፕሮጀክቱ በ2 ግብረ ኃይሎች የተከፈለ ሲሆን በትግበራው ግዜ ሰሌዳ መሰረትም ፕሮጀከቱ ሰኔ 30 ላይ ይጠናቀቃል። ፕሮጀክቱ የተመራቂ ተማሪዎችን መረጃ ማስገባት፣ ዲጅታል መጽሔቱን የማዘጋጀት እና ተደራሽ የማድረግ ዋና ዋና ግቦችን ይዞ የሚሰራ ይሆናል።

አጥቢያ ዶት ኮም ባለፈው የትምህርት ዘመን (2014 ዓ.ም.) በተመሳሳይ ትግበራ የተመራቂዎችን መጽሔት በጥራት እና በተፈለገው የጊዜ ሰሌዳ ማዘጋጀቱ እና ተደራሽ ማድረጉ ይታወሳል።