ቴክኖሎጂ ለቤተክርስቲያን
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የሚያመጣቸውን መልካም አጋጣሚዎች ለቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮ ማስፈጸሚያነት ለማዋል እንዲሁም ተግዳሮቶችን ለመቋቋም አጽንዖት ሰጥቶ መስራት ያስፈልጋል።
አጥቢያዎች ከምእመናን ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማዘመን በሁሉም ዘርፎች የተቀላጠፈ አገልግሎትን ለመስጠት እንዲያስችል ታልሞ ይህ መተግበሪያ ተዘጋጅቶልዎታል።
በቴክኖሎጂ የተደገፈ ውጤታማ የሆነ ተቋም ግንባታን ለመተግበር የግንዛቤ ማስጨበጫ፣ የመነሻ ጥናት፣ የግብአት ዝግጅት፣ የአተገባበር ስልት እና ቀጣይ ሞያዊ ድጋፍ ሊያስፈልግ ይችላል።
ስለአጥቢያ ዶት ኮም፣ ስለአገልግሎቶቻችን እና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ጥቆማወይም አስተያየትዎን ያካፍሉን። እርዳታ ቢያስፈልግዎም በፍጥነት ያሳውቁን።
የኦስሎ ማህደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ድረገጽ በአዲስ መልክ ተሻሽሎ ተለቀቀ!
የኦስሎ ማሕደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ድረገጽ በአዲስ መልክ ተሻሽሎ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት በዓል ምክንያት በማድረግ ተለቅቋል።
የስቶክሆልም ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን ድረገጽ ተሻሽሎ ቀረበ
ድረገጹ ከዚህ ቀደም በአጥቢያ ዶት ኮም የተሰራ ሲሆን የዶሜይን ስም እና የገጽታ ለውጥ በማድረጉ በአዲስ መልኩ እንዲሻሻል ምክንያት መሆኑ ታውቋል
የኦስሎ ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን የቴክኖሎጂ አገልግሎቱን ወደ አጥቢያ ዶት ኮም አዛወረ
በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ የሚገኘው ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤ/ክ ከዚህ ቀደም በፈቃደኛ አገልጋዮች ሲያስተዳደር የነበረውን የድረገጽ እና ተያያዥ የቴክኖሎጂ አገልግሎቶች ወደ አጥቢያ ዶት ኮም አዛውሯል።
የማኅበረ ቅዱሳን የ2015 ዓ.ም. ግቢ ጉባኤያት ተመራቂዎች ዲጅታል መጽሔት ስራ ተጠናቀቀ
በአጥቢያ ዶት ኮም ፕሮጀክት ተቋራጭነት የተሰራው የዚህ አመት (2015) የግቢ ጉባኤያት ተመራቂዎች ዲጅታል መጽሔት ስራ በታቀደለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ዛሬ ሐምሌ 8 ቀን 2015 ዓ.ም. ተጠናቀቀ።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ድረ-ገጽ ተለቀቀ
የሀገረ ስብከቱ ድረገጽ በብጹዕ አቡነ ኤርሚያስ ቡራኬ ዛሬ ሰኔ 6 ቀን 2015 ዓ.ም. ስራ ጀምሯል።