አገልጋይ የቴክኖሎጂ ባለሞያዎችን የማፍራት ስራ /Incubation Program/ የሙከራ ትግበራ ጀመረ

አጥቢያ ዶት ኮም ተተኪ ባለሞያዎችን ለማፍራት እና የአገልግሎቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የሚያስችል የማብቂያ መርሐግብር /Incubation Program/ የሙከራ ትግበራ ጀምሯል። በዚህ የሙከራ ትግበራ ተሳታፊዎችን ከሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እና ከማኅበረ ቅዱሳን ግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያ በተሰጡ የተሳታፊ ጥቆማዎች መነሻነት ምልመላ የተደረገ ሲሆን መርሐግብሩ ከ3-6 ወራትን የሚፈጅ ይሆናል።

የመርሐግብሩ ተሳታፊዎች በቴክኖሎጂ፣ ተቋማዊ አሰራር እና መፈሳዊ የሞያ አገልግሎት ዙርያ ስልጠናዎችን የሚወስዱ ሲሆን በአጥቢያ ዶት ኮም ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶች በመሳተፍ ተግባራዊ ልምምድ እንደሚያደርጉ ታውቋል።