የማኅበረ ቅዱሳን የ2015 ዓ.ም. ግቢ ጉባኤያት ተመራቂዎች ዲጅታል መጽሔት ስራ ተጠናቀቀ

በአጥቢያ ዶት ኮም ፕሮጀክት ተቋራጭነት የተሰራው የዚህ አመት (2015) የግቢ ጉባኤያት ተመራቂዎች ዲጅታል መጽሔት ስራ በታቀደለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ዛሬ ሐምሌ 8 ቀን 2015 ዓ.ም. ተጠናቀቀ። በፕሮጀክቱ ሒደት ልዩ ልዩ የሲስተም ማሻሻያ ስራዎች፣ ስልጠናዎች እና ሌሎች እንቅስቃሴዎች የተካሔዱ ሲሆን የዚህ አመት ዲጅታል መጽሔት በይዘት እና በጥራት ደረጃው ከፍ ያለ መሆኑ ታውቋል። ዲጅታል የምረቃ መጽሔቱ ለተመራቂዎች ከዛሬ ጀምሮ በስርጭት ላይ የሚገኝ ሲሆን በቀጣይም የግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያው የማስተዋወቂያ መርሐግብር እንደሚያዘጋጅ ታውቋል።።

አጥቢያ ዶት ኮም ለፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ መሳካት አስተዋጽዖ ያደረጉ የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት አስተባባሪዎች (በሁሉም እርከን ላይ የሚገኙ) ከፍ ያለ ምስጋናን ያቀርባል።