የድረገጽ አስተዳደር ሥልጠና ለትሮንዳሔም ምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተሰጠ

መጋቢት 20፣ 2016 ዓ.ም.

በኖርዌይ አገር ትሮንዳሔም ከተማ የሚገኘው የምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የቴክኖሎጂ ክፍልን በማቋቋም አሰራሮችን የማዘመን እና በቴክኖሎጂ የማስደገፍ እንቅስቃሴዎችን ጀምሯል። የዚህ እንቅስቃሴ አካል ከሆኑት ተፈጻሚዎች አንዱ በአጥቢያ ዶት ኮም ለብዙ አመታት በሙሉ ድጋፍ ሲተዳደር የነበረውን ድረገጽ የሚያስፈልገውን ስልጠና በመውሰድ በደብሩ ባለሞያዎች የማስተዳደር ስራ ነው። በዚሁም መሰረት በትናንትናው እለት (መጋቢት 20፣ 2016 ዓ.ም.) ለቴክኒክ ቡድኑ የመነሻ ስልጠና ተሰጥቷል።

በስልጠናው የይዘት አስተዳደር ሒደት እንዲሁም መረጃዎችን በድረገጹ የመለጠፍ፣ የማስተዋወቅ እንዲሁም የማንሳት በተግባር በመደገፍ ተካሒዷል። በቀጣይም በደብሩ የሚተገበሩ ልዩ ልዩ የቴክኖሎጂ ተፈጻሚዎች ሲኖሩ አጥቢያ ዶት ኮም በአማካሪነት እና ድጋፍ ሰጭነት የደብሩን አቅም የማጎልበት ስራን እንደሚሰራ ታውቋል።