የማኅበረ ቅዱሳን የ2014 ዓ.ም. ግቢ ጉባኤያት ተመራቂዎች ዲጅታል መጽሔት ስራ ተጀመረ

አጥቢያ ዶት ኮም የዚህን ዓመት /2014 ዓ.ም./ የማኅበረ ቅዱሳን ግቢ ጉባኤ ተመራቂዎች ዲጅታል መጽሔት ስራን ዓርብ ሚያዚያ 7/2014 ዓ.ም. በበይነ መረብ በተካሄደ የፕሮጀከት ማስጀመሪያ መርሐግብር ጀምሯል።

የትግበራ ፕሮጀክቱ በ3 ግብረ ኃይሎች የተከፈለ ሲሆን በትግበራው ግዜ ሰሌዳ መሰረትም ፕሮጀከቱ ሰኔ 30 ላይ የሚጠናቀቅ ሲሆን የተመራቂ ተማሪዎችን መረጃ ማስገባት፣ ዲጅታል መጽሔቱን የማዘጋጀት እና ተደራሽ የማድረግ ዋና ዋና ግቦችን ይዞ የሚሰራ ይሆናል። በፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሐግብሩ የአጥቢያ ዶት ኮም ባለሞያዎች፣ የማኅበረ ቅዱሳን አይ.ሲ.ቲ. ክፍል ተወካዮች፣ የግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያ እንዲሁም ሌሎች የማኅበረ ቅዱሳን ስራ አስፈጻሚ ተወካዮች እንደተገኙ ለማወቅ ተችሏል።