አገልጋይ የቴክኖሎጂ ባለሞያዎችን የማፍራት ስራ /Incubation Program/ የሙከራ ትግበራ ጀመረ

አጥቢያ ዶት ኮም ተተኪ ባለሞያዎችን ለማፍራት እና የአገልግሎቶችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የሚያስችል የማብቂያ መርሐግብር /Incubation Program/ የሙከራ ትግበራ ጀምሯል። በዚህ የሙከራ ትግበራ ተሳታፊዎችን ከሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እና ከማኅበረ ቅዱሳን ግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያ በተሰጡ የተሳታፊ ጥቆማዎች መነሻነት ምልመላ የተደረገ ሲሆን መርሐግብሩ ከ3-6 ወራትን የሚፈጅ ይሆናል።

የመርሐግብሩ ተሳታፊዎች በቴክኖሎጂ፣ ተቋማዊ አሰራር እና መፈሳዊ የሞያ አገልግሎት ዙርያ ስልጠናዎችን የሚወስዱ ሲሆን በአጥቢያ ዶት ኮም ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶች በመሳተፍ ተግባራዊ ልምምድ እንደሚያደርጉ ታውቋል።

የኦስሎ ማህደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ድረገጽ በአዲስ መልክ ተሻሽሎ ተለቀቀ!

የኦስሎ ማህደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ድረገጽ በአዲስ መልክ ተሻሽሎ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት በዓል ምክንያት በማድረግ ተለቅቋል። ድረገጹን ይህንን በመጫን ይመልከቱ

ድረገጹ በአጥቢያ ዶት ኮም ከተሰሩ ሌሎች የቤተርክርስቲያናችን ድረገጾች ጋር ወጥነትን ጠብቆ የተሰራ እንደሆነ ታውቋል። በቀጣይም ከድረገጽ ባለፈ የደብሩን አሰራሮች በቴክኖሎጂ የማስደገፍ ስራዎች እንደሚሰሩ ታውቋል።