ውጤታማ የስራ አመራር ስልጠና በኦስሎ ማህደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ተሰጠ

በኦስሎ ማህደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ለአምስት ተከታታይ ሳምንታት በበይነ መረብ የተሰጠው የውጤታማ ስራ አመራር ስልጠና በትናንትናው ዕለት ሚያዝያ 17 ቀን 2016 ዓ.ም. ተጠናቀቀ። በስልጠናው የተካተቱ የይዘት አርእስት የኢ/ኦ/ተ/ቤ፣ ባህል እና የለውጥ አመራር፣ ውጤታማ ተግባቦት፣ ውጤታማ ስብሰባ፣ በእቅድ መመራት፣ የአሰራር መመሪያ ዝግጅት እና ውጤታማ የጊዜ አጠቃቀም ሲሆኑ ስልጠናው በአጥቢያ ዶት ኮም ባለሞያዎች በሚሰጥ ገለጻ፣ ሰልጣኞችን ያሳተፈ ውይይት እና ተግባራዊ እንቅስቃሴዎችን ያካተተ እንደነበረ ታውቋል።

የደብሩ አስተዳዳሪ ቀሲስ ተስፋ ሚካኤል መኮንን በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ ገልጸዋል። ስልጠናው ብዙ ክህሎቶችን ያስጨበጠ ሲሆን በቀጣይም ወደ ትግበራ በመቀየር የአሰራር ማሻሻያዎችን ማስመግዘብ ይገባናል ብለዋል። በተጨማሪም በጅማሮ ላይ ያለው የደብሩ ስልታዊ እቅድ ዝግጅት ከአጥቢያ ዶት ኮም በሚደረገው ሞያዊ ድጋፍ የደብሩን ማኅበረሰብ አሳታፊ በሆነ መልኩ በልጽጎ ስራ ላይ እንዲውል እንሰራለን ብለዋል።

አጥቢያ ዶት ኮም በቀጣይ የክፍሎች አሰራር መመሪያዎች ዝግጅት እንዲሁም የቴክኖሎጂ ክፍልና የማዋቀር እና ስራ የማስጀመር ፕሮጀክቶችን ከደብሩ ሰበካ አስተዳደር ጉባኤ ጋር በመሆን የሚተገብር መሆኑም ተገልጿል።

ለሊቨርፑል መካነ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ኃይማኖት ቤ/ክ የተሰጠው የውጤታማ ሥራ አመራር ስልጠና ተጠናቀቀ

ለሰባት ተከታታይ ሳምንታት በበይነ መረብ የተሰጠው የውጤታማ ሥራ አመራር ስልጠና በትናንትናው እለት ተጠናቅቋል። በስልጠናው የተለያዩ መሰረታዊ ጉዳዮች የተዳሰሱ ሲሆን ስልጠናው በገለጻ፣ ውይይት እና ተግባራዊ እንቅስቃሴ የተደገፈ እንደነበር ታውቋል። የተሸፈኑት ዋና ዋና አርእስት፦ የኢ/ኦ/ተ/ቤ፣ ባህል እና የለውጥ አመራር፣ ባህል እና የለውጥ አመራር፣ ውጤታማ ተግባቦት፣ ውጤታማ ስብሰባ፣ በእቅድ መመራት እና የአሰራር መመሪያ ዝግጅት እንደሆኑ ታውቋል።

በመርሐግብሩ ማጠቃለያ ላይ የደብሩ አስተዳዳሪ ሊቀትጉኃን ቀሲስ ብርሃኑ ደሳለኝ ይህ የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ እድለኛ ነው። ውጤታማ ሥራን ለመስራት እና የበለጠ ለማገልገል የሚረዱ ክህሎቶችን ያስተዋወቀ ስልጠና አግኝቷል ብለዋል። እንዲሁም ለመርሐግብሩ ዝግጅት ቁልፍ የማስተባበር ስራን የሰሩት ቀሲስ ተመስገን ቅጣው ሰልጣኞች በስልጠናው ያገኟቸውን እውቀቶች በስራ ለመተግበር ሶስት ነገሮች ፡- ቁርጥ ውሳኔ፣ ትግበራ እና የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን መሻገር፣ ወደቀደመ አሰራሮች ላለመመለስ መታገል ያስፈልጋል ብለዋል

በመርሐግብሩ መዝጊያ ላይ አጥቢያ ዶት ኮም የስልጠናውን ቀጣይ ትግበራ የማገዝ እና የመከታተል ስራን የሚሰራ ሲሆን በቀጣይነትም ሌሎች ጉዳዮች ላይ ተመሳሳይ መርሐግብሮች ቀርጾ እንደሚንቀሳቀስ ተገልጿል።