በኢ/ኦ/ተ/ቤ ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ድረ ገጽ ተለቀቀ

 

በኢ/ኦ/ተ/ቤ ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ድረ ገጽ ተለቀቀ

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ፣ አገልግሎቱን ለማሳለጥ የሚያስችል መምሪያው ፫ኛውን ሀገር አቀፍ የስብከተ ወንጌል ቀን በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ እያከበረ ባለበት በዚህ የታሪካዊ ጉባኤ ላይ፣ www.eotceam.org የተሰኘውን አዲስ ድረ ገጽ በይፋ ሥራ መጀመሩ ተበሥሯል።
​ይኽ ድረ ገጽ ከሌሎች መሰል ድረ ገጾች ለየት የሚያደርገው የአገልግሎት አድማሱ ባለብዙ ቋንቋ አገልግሎት (Multilingual Support) ማለትም በአማርኛ፣ በኦሮምኛ፤ በትግርኛ እና በእንግሊዝኛ፣ቋንቋዎች የተዘጋጀ መኾኑ ተመላክቷል።
ይኽም ቤተክርስቲያን በሀገር ውስጥም ኾነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚገኙ ምእመናን በቋንቋቸው ትምህርተ ወንጌልን ለማድረስ የያዘችውን ስትራቴጂያዊ ግብ የሚያሳካ መኾኑ ተገልጿል። ድረ ገጹ በዋናነት ​​የምእመናንን ዕውቀት ለማሳደግና ለጥያቄዎቻቸው ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል፣ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን የጠበቁ መሠረታዊና ወቅታዊ ትምህርቶች እንዱኹም ዜናዎች፤ የቤተክርስቲያንን አጠቃላይ እንቅስቃሴ፣ የመምሪያውን የሥራ ክንውንና ወቅታዊ ክስተቶችን ለሕዝብ ተደራሽ የሚያደርግ መኾኑ ተነግሯል።
(ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ገጽ)