በኤ/ኦ/ተ/ቤ የስካንዲናቭያ እና ፊንላንድ ሀገረስብከት ድረገጽ ተሻሽሎ ተለቀቀ

በአጥቢያ ዶት ኮም አበልጻጊነት የተሰራው የሀገረስብከቱ ድረገጽ ትልቅ የሆነ የቴክኖሎጂ እና የገጽታ ማሻሻል ተደርጎበት ክለሳ 3 (version 3) ለተጠቃሚዎች ቀርቧል። በኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቢተክርስትያን የስካንዲናቭያ እና ፊንላንድ ሀገረስብከት ድረገጽ ለመጀመሪያ ጊዜ እ.ኤ.አ. በ2014 ዓ.ም. የተሰራ ሲሆን ሁለተኛ ማሻሻያ በ2019 እንደተደረገለት ታውቋል።

ከቴክኖሎጂ ተለዋዋጭነት አንጻር አጥቢያ ዶት ኮም ድረገጹን የማሻሻል እና የማዘመን ስራዎችን በየጊዜው እየሰራ መሔዱ ሁሌም እንደሚያስደስታቸው ሊቀ ካህናት ቀሲስ አፈወርቂ ተስፋ ገልጸዋል።