ውጤታማ እቅድ ዝግጅት በሚል ርዕስ ስልጠና እና የምክክር መርሐግብር ተካሔደ

ትናንት ሰኔ 19 ቀን 2014 ዓ.ም. “ውጤታማ እቅድ ዝግጅት” በሚል ርዕስ በአጥቢያ ዶት ኮም አስተባባሪነት በአለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤት አንድነት የስልጠና እና የምክክር መርሐግብር ተካሔደ።

በመርሐግብሩ 35 ተሳታፊዎች የታደሙ ሲሆን በአውደጥናት መልክ በውይይት እና ገለጻዎች በታጀበ መልኩ ተካሒዷል። በስልጠናው የተሸፈኑ አንኳር ነጥቦች፦
1. የእቅድ ምንነት እና አስፈላጊነት
2. በእቅድ ዝግጅት ዙሪያ ያሉ ጽንሰ ሐሳቦች
3. ወደ መሬት ለማውረድ የሚያግዝ የትግበራ ሒደት እና ተያያዥ ቅጾች

መርሐግብሩ መነሻ ግንዛቤን መፍጠር የቻለ ሲሆን በቀጣይ ሊሰራባቸው የሚገቡ አቅጣጫዎችንም ጠቋሚ ሆኗል። በተቋም ግንባታ ዙሪያ የሚሰጡ ስልጠናዎች እና የምክክር መርሐግብሮቹ ቀጣይነት እንደሚኖራቸው ተገልጿል።