የማኅበረ ቅዱሳን የ2016 ዓ.ም. ግቢ ጉባኤያት ተመራቂዎች ዲጅታል መጽሔት ስራ ተጠናቀቀ

በአጥቢያ ዶት ኮም ፕሮጀክት ተቋራጭነት የተሰራው የዚህ አመት (2016) የግቢ ጉባኤያት ተመራቂዎች ዲጅታል መጽሔት ስራ ከታቀደለት የጊዜ ሰሌዳ አስቀድሞ ትናንት ሰኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም.  የተጠናቀቀ ሲሆን የዲጅታል የምረቃ መጽሔቱ ለተመራቂዎች በስርጭት ላይ ይገኛል። የአመቱን የተመራቂዎች ዲጅታል መጽሔት በማስመልከት የግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያው የማስተዋወቂያ መርሐግብር እንደሚያዘጋጅ ታውቋል።

አጥቢያ ዶት ኮም ለፕሮጀክቱ መሳካት አስተዋጽዖ ያደረጉ የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት አስተባባሪዎች (በሁሉም እርከን ላይ የሚገኙ) ከፍ ያለ ምስጋናን ያቀርባል።