የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ይፋዊ ድረ-ገጽ ተለቀቀ !

በአጥቢያ ዶት ኮም የተስራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ይፋዊ ድረገጽ የ2015 ዓ.ም. ጥምቅት በዓልን ምክንያት በማድረግ ተለቀቀ።

ድረገጹ በቤተክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ማኅበራዊና ልማታዊ እንቅስቃሴዎች ዙሪያ ሕዝበ ክርስታያኑ በቴክኖሎጂ የታገዙ መረጃዎችን ማግኘት ይችል ዘንድ ሥራውን እንዲጀምር አድርጓል። በቀጣይም ድረገጹ በይዘት እየጎለበተ እንደሚሄድ እና መሰረታዊ፣ ወቅታዊ እንዲሁም ስልታዊነት ያላቸው መረጃዎ የሚለቀቁበት ዋናው ገጽ እንደሚሆን ታውቋል።