የሕጻናት እና አዳጊዎች ክፍል ውስጣዊ አሠራር መመሪያ በሸገር ከተማ ሃገረ ስብከት ደ/ኃ/ቅ/ሚካኤል ካቴድራል ፍሬ ስብሐት

በአጥቢያ ዶት ኮም ትብብር የተዘጋጀው የሕጻናት እና አዳጊዎች ክፍል ውስጣዊ አሠራር መመሪያ በሰንበት ት/ቤቱ ሥራ አመራር ጸድቆ የሙከራ ትግበራ ለማስጀመር ዝግጅት እንደተጀመረ ተገለጸ። የመመሪያ ዝግጅቱ በሕጻናት እና አዳጊዎች አገልግሎት ሱታፌ ያላቸው ልዩ ልዩ ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ሲሆን በዋናነት ከወላጆች መረጃዎችን በመጠይቅ እንዲሰበሰብ መደረጉ ታውቋል።

የተዘጋጀው መመሪያ በሙከራ የትግበራ ጊዜው የሚገኙ ልምድ እና ግብአቶችን በማካተት የሚሻል ሲሆን በቀጣይም ከሰንበት ት/ቤቱ የሌሎች ክፍሎች አሠራር መመሪያዎች ጋር እየተናበበ እንደሚተገበር ታውቋል።

በመመሪያው ዝግጅት የተሳተፉትን ሁሉ ከአጥቢያ ዶት ኮም እንኳን ደስ አላችሁ የሚል መልእክታችንን እናስተላልፋለን።